አሜሪካ
አሜሪካ በአገሯ የሚገኙት መኖሪያ ፍቃድ የሌላቸው ስደተኞች “ልክፈላችሁ ሂዱልኝ” ማለቷ ተሰማ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 16/04/2018፡- 3,000 ዶላር እሰጣችኋለሁ ፤ ነጻ በረራ ሁሉ አዘጋጃለሁ ብቻ እናተ በፍቃዳችሁ ምድሬን ለቃችሁ ውጡልኝ ” ስትል አሜሪካ በሀገሯ ለሚገኙ ሰነድ አልባ ስደተኞች መልዕክት አስተላልፋለች።
በ2026 መጨረሻ ላይ ከአሜሪካ በገዛ ፈቃዳቸው ለመውጣት ለሚፈልጉና በፈረንጆች እስከ ታህሳስ 31 ለሚመዘገቡ ስደተኞች ሀገሪቱ ነፃ በረራ እንዲሁም የ3000 ዶላር ክፍያም ይሰጣቸዋለሁ ብላለች።
በገዛ ፈቃዱ አልወጣም ያለ ስደተኛ ግን እስራት፣ በግዳጅ መባረር እንዲሁም ዳግም ወደ አሜሪካ ምድር መግባት እንዳይችል እገዳ እንደሚጣልበት ሀገሪቱ አሳውቃለች።



