መካከለኛ ምስራቅ

በኢራን ጦርነት 140 ገደማ የአሜካ ወታደሮች እንደተጎዱ ተገለጸ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 02/07/2018- አስራ አንደኛ ቀኑን በያዘው የኢራን ጦርነት፤ በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙ 140 ገደማ የአሜሪካ ወታደሮች እንደተጎዱ የአገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር ገለጸ።

የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ሻን ፓርኑል ባወጡት መግለጫ “ኦፕሬሽን ኢፒክ ፊውሪ ከተጀመረ አንስቶ ከ10 በላይ በሚሆኑ ቀናት በተፈጸሙ ተከታታይ ጥቃቶች 140 እንደሚደርሱ የተገመቱ የሠራዊት አባላት ተጎድተዋል” ብለዋል።

እንደ ፔንታጎን መረጃ ከእነዚህ ውስጥ “አብዛኛዎቹ ጉዳቶች አነስተኛ የሚባሉ” ናቸው። 108 ያህል የሠራዊት አባላትም ወደ መደበኛ ሥራቸው ተመልሰዋል ተብሏል።

“ስምንት የሠራዊት አባላት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ከፍተኛ ደረጃ ያለው ሕክምና እያገኙ ነው” ብለዋል።

በአሜሪካ እና እስራኤል ዘመቻ የተከፈተባት ኢራን በወሰደችው የአጸፋ ጥቃት በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙ አሜሪካ የጦር ሰፈሮችን ዒላማ አድርጋለች። ጦርነቱ በተጀመረ ማግሥት ኩዌት ውስጥ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ስድስት አሜሪካውያንን መገደላቸው ይታወሳል።

ከጦር ሠፈሮችም በተጨማሪ ኢራን በባሕረ ሰላጤው አገራት የሚገኙ ሆቴሎችን፣ አየር ማረፊያዎችን፣ የነዳጅ መሠረተ ልማቶችን አጥቅታለች።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates