ኢትዮጵያ እና ኬንያ የድንበር ኮሪደሩን ለማስጠበቅ የጋራ ወታደራዊ ዘመቻ ለመጀመር መስማማታቸው ተሰማ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 25/06/2018፡- ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሞያሌ-ማርሳቢት-ቱርካና ኮሪደር ላይ የፀጥታ ቅንጅትን ለማጠናከር መስማማታቸው የተገለፀ ሲሆን ድንበር ተሻጋሪ ስጋቶችን ለመፍታት እና ሁለቱን ሀገራት የሚያገናኙ ቁልፍ መሠረተ ልማቶችን ለመጠበቅ የጋራ ወታደራዊ ስራዎችን እንደሚሰሩ ተገልፀዋል።
ስምምነቱ በሁለቱ ጎረቤቶች መካከል ያለውን የመከላከያ ትብብር ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ የታደሱ ጥረቶች አካል ነው ተብለዋል።
በስምምነቱ መሰረት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የመከላከያ ኃይል እና የኬንያ የመከላከያ ኃይል ተጋላጭ የሆኑ የድንበር አካባቢዎችን እና ስትራቴጂካዊ ሀብቶችን ኢላማ በማድረግ ደረጃ በደረጃ እና በተቀናጀ መልኩ ስራዎችን እንደሚያከናውኑ ይጠበቃል።
ይህ በጋራ ስራዎች እና በመሠረተ ልማት ጥበቃ ላይ የተደረገው አዲስ ትኩረት በኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ ሙሳ እና የኬንያ የመከላከያ ካቢኔ ፀሐፊ ሶይፓን ቱያ መካከል ከፍተኛ ደረጃ ያለው የሁለትዮሽ ውይይት ተከትሎ ነው።
ስብሰባው የተካሄደው በአዲስ አበባ ታሪካዊው የአድዋ ጦርነት 130ኛ ዓመት መታሰቢያ መሆኑን ተገልፀዋል።
ሁለቱም አመራሮች የላፕሴት ኮሪደርን ጨምሮ የስትራቴጂካዊ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጥበቃ ለማሳደግ ሊወሰዱ ስለሚገባ እርምጃዎችን የተወያዩ ሲሆኑ፣ ይህም የላሙ ወደብ-ደቡብ ሱዳን-ኢትዮጵያ የትራንስፖርት ኮሪደርን ጨምሮ፣ በአፍሪካ ቀንድ ለንግድ፣ ለኢነርጂ ትራንስፖርት እና ለግንኙነት ማዕከላዊ ወሳኝ ክልላዊ ውህደት ተነሳሽነት እንደሆነ ተገልጸዋል።
አገራት የመጀመሪያውን የጋራ መከላከያ ኮሚቴ ውጤት ለማፋጠን ደረጃ በደረጃ እና ተግባራዊ ማዕቀፍ ለማፅደቅ እንደተስማሙ የተገለፀ ሲሆን ባለስልጣናቱ ትኩረቱ ተግባራዊ በሚደረግ የጸጥታ ትብብር ላይ እንደሚሆን አመልክተዋል።
በሞያሌ-ማርሳቢት-ቱርካና ኮሪደር ላይ ያለው ደህንነት ድንበር ተሻጋሪ የወንጀል መረቦች፣ በሀብት ላይ የተመሰረቱ ግጭቶች እና የታጠቁ ቡድኖች እንቅስቃሴ ምክንያት የጋራ ስጋት እንደሆኑም ተለይተዋል፡፡



