ዲፕሎማሲ
የሳውዲ ዓረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ መካከለኛ አፍሪካ ሪፐብሊክ በማምራት ከአገሪቱ ፕሬዝዳንት ተወያዩ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 18/06/2018፡- የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ፋውስቲን-አርቻንጅ ቱዋዴራ የሳውዲው ውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ዋሊድ አብዱልከሪም አል ካሪጅን ተቀብሎ አነጋግረዋል፡፡
የሳዑዲ_ዓረቢያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ጉብኝ አድርጎ እንደነበር ይታወሳል፡፡
የሳዑዲ ዓረቢያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሊድ አብዱልከሪም አል ካሪጅ፣ በአስመራ ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር ከተወያዩ ከአንድ ሳምንት በኋላ አዲስ አበባ በመግባት ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋር ተገናኝተው መምከራቸው ይታወሳል።
ሳውዲ ዓረቢያ በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባሀር ያላትን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከፍተኛ ዲፕሎመሲያዊ ጥረት እያደረገች እንደሆነች ይገለፃል፡፡



