አፍሪካ

ቱርክ ታሪካዊት የተባለላትን ነዳጅ ቆፋሪ መርከቧን ወደ ሶማሊያ መላኳ ታወቀ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 09/06/2018፡- ቱርክ እሁድ ዕለት ጥልቅ ነዳጅ ቆፋሪ የሆነውን መርከቧን ለመጀመሪያ ተልዕኮው ወደ ሶማሊያ መላኳን አስታውቃለች።

የቱርክ የኢነርጂ እና ተፈጥሮ ሐብት ሚኒስትር አልፓስላን ባይራካታር እርምጃውን ታሪካዊ ብለውታል።

መርከቧ ከ45 ቀናት ጉዞ በኋላ ሞቃዲሾ ደርሳ ቁፋሮውን እንደምትጀምር ተነግሯል።
ቱርክ እና ሶማሊያ እ.አ.አ በ2014 በባሕር እና በባሕር ዳርቻ ላይ የነዳጅ እና ጋዝ ፍለጋ ለማከናወን ተስማምተዋል።
አሁን የተላከችውን መርከብ ጨምሮ ነዳጅ የሚቆፍሩ የቱርክ መርከቦች ቁጥር ስድስት መድረሱን ሚኒስትሩ ተናግረዋል ሲል የቱርክ የዜና ወኪል አናዶሉ ዘግቧል።
ቱርክ ግዙፍ የባሕር ዳርቻ ነዳጅ ፍለጋ በማካሄድ ከዓለም አራተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝም አክለው ተናግረዋል።
ከአዲሱ የጎርጎሮሳዊያን ዓመት ወዲህ አገሪቱ በጋዝ እና ነዳጅ ፍለጋ ላይ ከተሰማሩ የአሜሪካ እና ዩናይትድ ኪንግደም ኩባንያዎች ጋር ስልታዊ ስምምነት አድርጋለች።
Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates