አፍሪካ

የግብፅ መንግስት ወደ ሶማሊያ የሚልከውን የመካከያ ሐይል በካይሮ ለትርኢት አቀረበ፡፡

በሌላ በኩል አልሸባብ ትናንት ባደረገው ውጊያ ተሽከርካሪዎችንና የጦር መሳሪያዎችን መያዙን ተናገረ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 04/06/2018፡- የግብፅ የመከላከያ ሚኒስቴር የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃመድ በዚህ ሳምንት ካይሮ ከጎበኙ ከጥቂት ቀናት በኋላ የአፍሪካ ህብረት  ተልዕኮ አካል ሆነው ወደ ሶማሊያ እንደሚሰማሩ የተገለፀላቸውን  ወታደሮችና ወታደራዊ መሳሪያዎችን፣ አውሮፕላኖችን ጨምሮ የሚያሳይ ቪዲዮ አውጥቷል።

ይህ በእንዲህ እያለ አልሸባብ በባርሳንጉዩኒ አቅራቢያ በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ተሽከርካሪዎችንና የጦር መሳሪያዎችን መያዙን ተናገረ፡፡

አልሸባብ ማክሰኞ ዕለት በደቡብ ሶማሊያ በታችኛው ጁባ ክልል ባርሳንጉዩኒ አካባቢ በፈጸመው ጥቃት ተሽከርካሪዎችንና የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን መያዙን የሚያሳዩ ምስሎችን አውጥቷል።

በሚዲያ ቻናሎቹ በተሰራጨው መግለጫ፣ በጥቃቱ 32 የጁባላንድ ወታደሮች መገደላቸውን ተናግሯል።

የጁባላንድ ባለስልጣናት ግን ዘገባውን ውድቅ አድርገውታል፣ ኃይላቸው ጥቃቱን እንዳከሸፈ እና በታጣቂዎቹ ላይ ከባድ ጉዳት እንዳደረሰ ተናግረዋል። ምንም ይፋዊ የጉዳት አሃዝ ግን አልተሰጠም።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates