አፍሪካ

የሱዳን ጦር የፈጣን ድጋፍ ሐይል የአየር መከላከያ መሳሪያዎች እንዳወደመ ተገለፀ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 04/06/2018፡- የሱዳን ጦር ኃይሎች በአገሪቱ ውስጥ በተለያዩ ክፍሎች በሲቪሎች እና በሲቪል ተቋማት ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ስያገለግሉ ነበር ያለቻቸው በርካታ ጠላት ድሮኖችን በተሳካ ሁኔታ ለይተው ማውደሙ ይፋ አድርገዋል።

የጦር ኃይሎች ምንጮች እንደዘገቡት የአየር መከላከያ ክፍሎች ውጤታማ በሆነ መንገድ እንደተመቱ እና በታጣቂው ላይ ትልቅ የማተሪያል ኪሳራ ማድረሱን አስታውቀዋል፡፡

ድሮኖቹ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ለመምታት በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ እንደዋሉ የጠቆሙት ምንጮች፣ በዚህም በሲቪሎች ላይ ሞት እና ጉዳት አስከትሏል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተፈጸሙት ጥቃቶች አንዱ በኮርዶፋን በሚገኝ የሰብአዊ እርዳታ ኮንቮይ ላይ ያነጣጠረ ሲሆን የእርዳታ አቅርቦቶች ለተቸገሩ ሰዎች እንዳይደርሱ እና የተጎዱ ማህበረሰቦችን ስቃይ ለመጨመር ዳርገዋል ብለዋል።

ጥቃቶች የአቅርቦት መስመሮችን እና የሰብአዊ ስራዎችን በመምታት የእርዳታ ድርጅቶች አስፈላጊ አገልግሎቶችን እንዳያቀርቡ አስተጓል ሲሉ የሱዳን ጦር ቃል አቀባይ ተናግረዋል፡፡

እነዚህ በሲቪሎች እና በሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ተደጋጋሚ ጥቃቶች ንፁሃን ሰዎችን ኢላማ ማድረግ ወይም የሰብአዊ ስራን ማደናቀፍ የሚከለክሉ ዓለም አቀፍ ህጎችን እና ደንቦችን በግልጽ መጣስን ያመለክታሉ።

በሲቪሎች እና በሰብአዊ እርዳታ ኮንቮዮች ላይ ሆን ተብሎ ኢላማ ማድረግ የዓለም አቀፍ የሰብአዊነት ህግን ከባድ ጥሰት ያሉት ቃል አቀባዩ እነዚህን ጥቃቶች የሚፈጽሙ እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርጉ እና የሚያስታጥቁ አካላት ለሚደርስባቸው መዘዝ ሙሉ ኃላፊነት ይወስዳሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates