አፍሪካ

የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና የፀጥታ ምክር ቤት እስራኤል ለሶማሌላንድን እውቅና መስጠቷ በማውገዝ፣ ‘ወዲያውኑ እንዲሰረዝ’ ጥሪ አቅርቧል።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 30/04/2018፡- የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና የፀጥታ ምክር ቤት እስራኤል ለሶማሌላንድ የሰጠችኽን እውቅና “በጥብቅ” በማውገዝ፣ እርምጃው ወዲያውኑ እንዲሰረዝ እና የሶማሊያን ሉዓላዊነት፣ አንድነት እና የግዛት አንድነት እንዲያረጋግጥ ጥሪ አቅርቧል።

ከትናንትና በስትያ በተካሄደው 1324ኛው የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ በኋላ ባወጣው መግለጫ፣ ምክር ቤቱ “እስራኤል ‘ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ’ የተሰጠውን የአንድ ወገን እውቅና አጥብቆ በማውገዝ ወዲያውኑ እንዲሰረዝ ጥሪ አቅርቧል።

ምክር ቤቱ ይህን ውሳኔ የወሰነው “ለሶማሊያ ፌዴራል ሪፐብሊክ ሉዓላዊነት፣ አንድነት፣ የግዛት አንድነት እና መረጋጋት የማይናወጥ ቁርጠኝነት” እንዳለው በማረጋገጥ፣ ይህም በአፍሪካ ህብረት ህግ፣ የሰላም እና የፀጥታ ምክር ቤትን ማቋቋም በተመለከተ ባለው ፕሮቶኮል እና በተባበሩት መንግስታት ቻርተር ላይ ያለውን አቋም መሰረት በማድረግ ነው።

“ማንኛውም ተዋናይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገርን የግዛት አወቃቀር የመቀየር ስልጣን ወይም ህጋዊ አቋም የለውም” ሲል ምክር ቤቱ በማከል “እንደዚህ አይነት መግለጫ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት ባዶ እና የተሰረዘ ነው” ብሏል።

ምክር ቤቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ቀደም ሲል የወሰዱትን አቋም በደስታ መቀበለውም አረጋግጧል።

እንዲህ ያሉት እርምጃዎች “የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት መሰረታዊ መርሆዎችን የሚቃረኑ እና በአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ላይ ሰፊ አንድምታ ያለው አደገኛ ምሳሌ የመፍጠር አደጋን ሊያስከትሉ ይችላሉ” ሲል አስጠንቅቋል።

በተጨማሪም “በ2063 አጀንዳ ላይ እንደታሰበው የተቀናጀ፣ የበለፀገ እና ሰላማዊ አፍሪካን ወደመፍጠር የሚደረገውን እድገት ያዳክማል” ሲል ምክር ቤቱ አስታውቋል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates