አፍሪካ

ሱዳን ከበፊት ዛሬ በተሻለ ቁመና ትገኛለች ሲሉ ጄነራል አል ቡርሃን አስታወቁ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 20/04/2018፡- የሱዳን ሽግግር ሉዓላዊነት ምክር ቤት ሊቀመንበር ጄነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን ሰሙኑን ከቱርኪው ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጠይብ ኦርዶሃን መወያየታቸው የሚታወስ ሲሆን በአንካራ በተካሄደው የፕሬስ ኮንፈረንስ ላይ እንዲህ ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ለወዳጆቻችን ብለን ለምናስባቸው አገሮች እና ሱዳን ደካማ እና የተሳሳቱ እርምጃዎችን ለመውሰድ ለሚዘጋጁ ሰዎች ግልጽ መልእክት አለኝ ያሉት ሲሆን ሱዳን ዛሬ ከበፊቱ የበለጠ ጠንካራ ነች፣ እና ጥንቃቄ ማድረግ እና  ወደ ስህተቶች ከመውደቅ በፊት ወደ ኋላ መመለስን ይጠይቃል፣ የሚከተሉት መዘዞች ውድ ይሆናሉ ብለዋል።

ከአንድ አመት በፊት ከተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ፕሬዝዳንት መሐመድ ቢን ዛይድ ጋር ቀጥተኛ ውይይቶች እንደተካሄዱ የገለፁት አል ቡርሃን፣ በዚህ ወቅት በሱዳን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ለማስቆም ቃል ገብቶ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

ይህ ቃል ግን አልተከበረም፣ እናም ለተገባው ቃል ምንም አይነት ቁርጠኝነት ሳይኖረው ተመሳሳይ እርምጃ ቀጥሏል ብለዋል።

ጄነራል አልቡርሃን ከፕሬዝዳንት ኦርዶሃን ጋር ባደረጉት ውይይት ቱርክ የሱዳንን ሰላምና መረጋጋት እንዲረጋገጥ የበኩልዋን ጥረት እንደታደርግ መጠየቃቸው የተገለፀ ሲሆን ሆኖም ከፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሐይሉ ጋር የሚደረግ ውይይት አሁንም እንደማይቀበሉት ማረጋገጣቸው ተሰምተዋል፡፡

እንደ ጄነራል አልቡርሃን አባባል ሱዳን የፈጣን ድጋፍ ሐይሉ ታጣቂ ቦታዎች በያዘበት ሰዓት የሚደረግ ድርድር ውጤት የለውም የሚል ነው፡፡

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates