የተለያዩ

በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር የተከሰሰ ኤርትራዊ ወደ ኔዘርላንድስ ተላልፎ ተሰጠ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 16/04/2018፡- የሰዎች ሕገወጥ አዘዋዋሪ ንጉሥ እንደሆነ የተነገረለት ኤርትራዊ ረቡዕ ዕለት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ወደ ኔዘርላንድስ ተላልፎ መሰጠቱ የተገለፀ ሲሆን ጉዳዩ በኔዘርላንድስ ፍርድ ቤት ችሎት ይታያል ተብሏል።

የ41 ዓመቱ ኪዳኔ ዘካሪያስ ሃብተማርያም እ.አ.አ. በ2021 በኢትዮጵያ ችሎት ላይ እያለ ከሸሸ በኋላ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚፈለጉ ተጠርጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ እንደነበር የኔዜርላንድስ የህዝብ አቃቤ ህግ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ተጠርጣሪው በኔዘርላንድስ በስደተኞች ሕገወጥ ዝውውር፣ በማገት፣ በዝርፊያ፣ በዓመፅ እና በጾታዊ ጥቃት እንዲሁም የወንጀል ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ ወንጀሎች ይፈለጋል።

ጉዳዩ ባለፈው ወር በኔዘርላንድስ ፍርድ ቤት ከተከፈተው ክስ ከሌላ ኤርትራዊ ሰው ተወልደ ጎይቶም ጋር የተያያዘ ሲሆን አቃቤ ህጎች የ20 ዓመት እስራት እንደጠየቁ ይታወሳል።

ይህ በኔዘርላንድስ እስካሁን ከቀረቡት ትላልቅ የሰው ልጅ ሕገወጥ አዘዋዋሪ ጉዳዮች አንዱ ነው ሲሉ አቃቤ ህጎች ተናግረዋል።

ጎይቶም ለዳኞች በስህተት የማንነት ሰለባ መሆኑን ተናገሯል።

ኪዳነ በ2023 በሱዳን በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሚመራ ዓለም አቀፍ አደን ተከትሎ የተያዘ ሲሆን መጪው ቅዳሜ የመጀመሪያ ችሎት ለማቅረብ ቀጠሮ ተይዟል።

የኔዘርላንድስ አቃቤ ህግ ባወጣው መግለጫ ሁለቱ ኤርትራውያን “ተባብረው በመስራት እና በዋናነት ኤርትራውያን ስደተኞችን በማጥቃት እና በማስገደድ ከፍተኛ ገንዘብ እንዳገኙ” ገልጿል።

ኪዳነ በኢትዮጵያ በሰዎች ህገወጥ ዝውውር ክስ ችሎት ላይ እያለ ከእስር ቤት ካመለጠ በኋላ በሌለበት ጥፋተኛ ሆኖ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates