መካከለኛ ምስራቅ
በጋዛ የሚንቀሳቀሰው ሐማስ «መልሶ እየተደራጀ» ነው ሲሉ እስራኤልን የጎበኙት የአሜሪካው ሴናተር ሊንድሰይ ግርሃም ወነጀሉ።
ሴናተሩ ሒዝቦላህንም በተመሳሳይ ወንጅለዋል።

ኢትዮ ሞኒተር፡13/04/2018፡- ሴናተሩ እንዳሉት «በተኩስ አቁም ስምምነቱ መሠረት ሐማስ ትጥቁን መፍታት ሲገባው መልሶ እየተደራጀና እየታጠቀ ነው» ሲሉ ወቅሰዋል። ይህም ተቀባይነት እንደሌለው አክለዋል።
እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በሕዳር ወር 2024 ዓ.ም በእስራኤልና ሒዝቦላህ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ቢፈረምም በተለያዩ ጊዚያት ለሚፈጸሙ የስምምነቱ ጥሰቶች አንዱ ሌላኛውን ይወነጅላሉ ሲል የዘገበው የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ነው።
እስራኤልም አለፎ አልፎ የምታደርጋቸው ጥቃቶች እንደቀጠለች ስትሆን በእየርሳሌም ድንበር ሕገ ወጥ ግንባታወች አጠናክራ መቀጠሏ መረጃዎች ያሳያሉ።



