አፍሪካ

ሶስት ሚሊዮን ሱዳናውያን ወደ አገራቸው ሲመለሱ የተፈናቀሉትን ቁጥር በአምስት ደረጃ ቀንሰዋል ሲል ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(IOM) አስታወቀ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 09/04/2018፡- በሱዳን ወደ አገራቸው የሚመለሱ ሰዎች ቁጥር ከሶስት ሚሊዮን በላይ ሆኗል፣ ይህም በአገሪቱ ውስጥ የተፈናቀሉትን ሰዎች ቁጥር በ19% ቀንሷል ሲል ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት (IOM) ረቡዕ ዕለት አስታውቋል።

በ18ቱ ግዛቶች ውስጥ ከ12,000 በላይ ቦታዎችን ባጠናው የቅርብ ጊዜ የሱዳን መፈናቀልና የመመለሻ አጠቃላይ እይታ፣ ድርጅቱ በ11.5 ሚሊዮን የነበረው የስደተኞች ቁጥር ወደ 9.33 ሚሊዮን ዝቅ ብሏል ሲል አመልክተዋል።

ከ3,027,446 ጠቅላላ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መካከል 81% የሚሆኑት ሲመለሱ 19% ደግሞ ከውጭ ተመልሰዋል ብለዋል መረጃው።

ኤጀንሲው ባለፈው ወር ብቻ የሚፈናቀሉት ሰዎች ቁጥር በ16% መቀነሱን በመግለፅ፣ ይህም የሱድን ሰራዊት በሰናር፣ አጅ ጃዚራ እና ካርቱም ውስጥ ቁልፍ ቦታዎችን መልሶ በመቆጣጠር ምክንያት ነው ብለዋል።

ወደ ቀያቸው የሚመለሱ ዜጎች እየጨመረ ቢመጣም፣ ብዙዎች በስራ እጥረት እና በተፈናቃዮች አካባቢዎች ደካማ ሁኔታዎች ምክንያት ወደ ኋላ እየተመለሱ መሆኑን አስጠንቅቋል፡፡

ሪፖርቱ ከባድ የሰብአዊነት ክፍተቶችን እና መሰረታዊ ፍላጎቶችን የማግኘት እጦትን አጉልቶ አሳይቷል።

የምግብ ዋስትናን በተመለከተ፣ 32% የተፈናቃዮች ቤተሰቦች እና 20% የተመለሱ ቤተሰቦች ባለፈው ወር ሙሉ ቀን እና ሌሊት ምግብ ሳይበሉ እንደቆዩ ሪፖርት አደርገዋል።

የጤና አጠባበቅ አሁንም ትልቅ ፈተና ሆኖ ቀጥሏል፣ 46% የተፈናቃዮች ቤተሰቦች እና 20% የተመለሱ ቤተሰቦች አስፈላጊውን የህክምና አገልግሎት ማግኘት አለመቻላቸው ጠቅሰዋል፡፡

ካርቱም ከፍተኛውን የተመላሾች ቁጥር አስመዝግቧል፣ ከ1.09 ሚሊዮን በላይ ተመዝግቧል።

በ12 ግዛቶች መፈናቀሉ ቢቀንስም፣ በሰሜን፣ በምዕራብ፣ በምስራቅ እና በመካከለኛው ዳርፉር እንዲሁም በኮርዶፋን ክፍሎች መጨመሩን ቀጥሏል ሲል የዓለም ፍልሰተኞች ድርጅት አስታውቀዋል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates