አፍሪካ

የአፍሪካ መብቶች ኮሚሽን የኤርትራ መንግስት በአፋር ማህበረሰብ ላይ ፈፀማቸው በተባለው በደል ክስ መመስረቱ ታወቀ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 203/04/2018፡- የአፍሪካ የሰብአዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን በኤርትራ መንግስት ላይ የከፈተውን ክስ በቀይ ባህር አፋር ዴሞክራቲክ ድርጅት (RSADO) ባቀረበው አቤቱታ ተመስርቶ እንደሆነ ቡድኑ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ሰኔ 4 ቀን 2025 የቀረበው አቤቱታ በኤርትራ #ዳንካሊያ ክልል ውስጥ በሚገኙ የአገሬው ተወላጅ ቀይ ባህር አፋር ሕዝቦች ላይ የተፈፀመውን ሰፊ ​​እና ስልታዊ ጥሰቶች ይጠቅሳል።

እንደ RSADO ገለጻ፣ የአፋር ማህበረሰብ ለረጅም ጊዜ መፈናቀል፣ ስደት፣ ከህግ አግባብ ውጭ ግድያዎች፣ አስገዳጅ መጥፋት እና በቀይ ባህር ዳርቻ ላይ የአባቶች መሬቶች መውረስን ጨምሮ “በመንግስት የተጠነሰሱ” ጥሰቶች አጋጥመውታል ብሏል።

በዚህም ኮሚሽኑ በምርመራዎች ተመስርቶ ክስ መመስረቱን ያስታወቀው ድርጅቱ ይህም ወደ ዓለም አቀፍ ተጠያቂነት ለማሸጋገር ወሳኝ እርምጃ አድርጎ እንደሚመለከተው ገልጿል።

የአፋር ማህበረሰብ ችግር “ከእንግዲህ በኃላ አይደበቅም ወይም ችላ እንደማይባል” የሚያሳይ አመላካች እንደሆነ የጠቀሰው ቡድኑ ኮሚሽኑን ፈጣን እና መርህ የተሞላበት ምላሽ ብሎ ለጠራው ነገር አድናቆቱን ገልፆ ጉዳዩ ተቀባይነት እና ብቁነት ደረጃ ላይ ሲደርስ ሙሉ ትብብር ለማድረግ ቃል ገብቷል።

RSADO በጉዳዩ ማስረጃዎችን፣ ሰነዶችን እና ምስክርነቶችን ለማቅረብ እቅድ እንዳለው ተናግሯል።

ድርጅቱ የአፍሪካ መንግስታት፣ የክልል አካላት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በኤርትራ ላይ ጫና እንዲጨምሩ እና በቀይ ባህር አፋር ህዝብ ላይ የሚደርሰውን ተጨማሪ በደል ለመከላከል እርምጃዎችን እንዲወስዱ አሳስቧል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates