ዲፕሎማሲ

የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለትራምፕ መልስ መስጠት አሰፈላጊ አለመሆኑ ተናገሩ።

"ትራምፕ የሚሰድቡት እኛን ብቻ አይደለም" ሲሉም ተደምጧል።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 26/03/2018፡- የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማክሰኞ ዕለት በዋይት ሀውስ የካቢኔ ስብሰባ ላይ የሶማሊያ ስደተኞችን “ቆሻሾች” ብለው መጥራታቸውን ተከትሎ “መልስ አለመስጠት ይሻላል” ሲሉ የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ባሬ መናገራቸው ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ዘግቧል።

ባሬ በሞቃዲሾ በተካሄደው የፈጠራ ጉባኤ ላይ በሼበሌ ቲቪ የተላለፈውን መግለጫ በተመለከተ ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ እንዳልሆኑ በመግለፅ “ትራምፕ የሚሳደበው እኛን ብቻ አይደለንም፤ አንዳንድ ጊዜ ምላሽ አለመስጠት ይሻላል” ብለዋል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለካቢኔያቸው የሶማሊያ ስደተኞችን በአሜሪካ እንደማይፈልጉ በመግለጽ አገሪቱ “እየሸተተች” ስለሆነች የሶማሊያ ስደተኞችን መቀበል አገሪቱን “በተሳሳተ መንገድ እንደሚወስድ” ተናግረዋል።

አንዳንድ ሶማሊያውያን የመንግስታቸውን ምላሽ አለመስጠት ተችተዋል። አብዱላሂ ኦማር የተባሉ ነሞቃዲሾ ነጋዴ “የሶማሊያ መሪዎች እና ፖለቲከኞች አገሪቱን እና ብሔራዊ ጥቅሞችን መጠበቅ አለባቸው። ትራምፕ ለሕዝባችን ስላለው የጥላቻ ንግግር አፍዎን ለምን ዝም አላችሁ?” ብለዋል።

በሞቃዲሾ የሚገኘው የግራፊክ ዲዛይነር አሊ ያህዬ በበኩሉ “እኛ ቆሻሻ አይደለንም። የትራምፕ አስተያየቶች መሠረተ ቢስ ናቸው፤ በአሜሪካ ያለው የሶማሊያ ማህበረሰብ ለአገሪቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል” ሲል ተናግሯል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates