አፍሪካ

የሱዳን ጦር በኤል ፋሸር ዋና ዋና ቦታዎችን ከፈጣን ድጋፍ ሰጪው ሐይል መልሶ መቆጣጠሩን አስታወቀ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 28/01/2018፡- የሱዳን ጦር በመግለጫው እንዳስታወቀው በኤል ፋሸር ታጣቂ ሐይሉ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ጥቃት ፈፅሞ በሰው እና በመሳሪያዎች ላይ ጉዳት አድርሷል ብሏል።

የሱዳን ጦር በምእራብ ሱዳን የሰሜን ዳርፉር ግዛት ዋና ከተማ በሆነችው ኤል ፋሸር ውስጥ በፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሃይሎች የተያዙ በርካታ  ቦታዎችን መያዙን አስታውቋል።

የወታደራዊ መግለጫው ማክሰኞ እንዳስታወቀው የሰራዊቱ ሃይሎች በርካታ የ RSF “የመከላከያ ቦታዎችን” ለማጽዳት “ልዩ ስራዎችን” በማካሄድ በአማፂ ቡድኑ ላይ የሰው ሐይል እና የመሳሪያ ኪሳራዎችን አድርሻለሁ ብሏል።

ቁጥሩን በትክክል ሳይገልፅ በርካታ የውጊያ ተሽከርካሪዎችን መማረካቸውን እና ሌሎች ስድስት ታጣቂ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ መውደማቸውንም ጦሩ አስታውቋል።

በጦር ሠራዊቱ መግለጫ ላይ ከRSF ምንም አስተያየት አልሰጠም።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates