ዲፕሎማሲ
“ቻይናን ታይዋን ላይ ኃይል እንዳትጠቀም ካደረጉ ትራምፕ የኖቤል ሽልማት ይገባቸዋል” ሲሉ የታይዋን ፕሬዝዳንት ተናገሩ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 28/01/2018፡- የታይዋን ፕሬዝዳንት ላይ ቺንግቴ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ዢንፒንግ በታይዋን ላይ የሚወስደውን የሃይል እርምጃ እንዲተው በተሳካ ሁኔታ ካሳመኑ የኖቤል የሰላም ሽልማት ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል።
ይህን የተናገሩት ዘ ክሌይ ትራቪስ እና ባክ ሴክስተን ሾው በተባለው የአሜሪካ ወግ አጥባቂ የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ በተደረገላቸው ቃለ ምልልስ ወቅት ነው።
ቻይና እንደግዛት ይገባኛል የራሴ አካል ናት ስትል ታይዋን ትገልጼለች።
ሁለቱ ወገኖች መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባይኖራቸውም ታይዋን ለደህንነት ድጋፍ በሚል በአሜሪካ ላይ ከፍተኛ ጥገኛ ነች።
በ2025 ዓመት መጀመሪያ ላይ ወደ ስልጣን የተመለሱት ትራምፕ እስካሁን ከታይፔ ጋር ምንም አይነት አዲስ የጦር መሳሪያ ስምምነቶችን ይፋ አላደረጉም።
የፕሬዝዳንት ላይ አስተያየት የተሰማው ለአሜሪካ-ቻይና-ታይዋን ግንኙነት በጣም አስቸጋሪ በሆነ ጊዜ ላይ ነው።
በታይዋን ባህር ውስጥ ያለው ውጥረት እየጨመረ በመምጣቱ ቻይና በደሴቲቱ ዙሪያ ወታደራዊ ልምምዶችን አጠናክራለች፣ በሁለቱም የምስራቅ ቻይና ባህር እና ደቡብ ቻይና ባህር ላይ የቻይና ኃይል መገኘቱን በማስፋፋት የታይዋን እይታ ምናልባትን ቻይና ለጥቃት ዝግጅት እያደረገች ነው የሚል ስጋት ፈጥሯል።