ኢትዮጵያፖለቲካ

አቶ ጌታቸው ረዳ “የህወሐት አመራሮች ሻዕቢያን ለማዳን የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለመግታት መስዋእት እከፍላለሁ” ሲሉ ተናገሩ።

ኤርትራ በራሷ ኢትዮጵያን መግጠም ስለማትችሉ  የህወሐት አመራሮችን እየተጠቀመች መሆኗም ከሷል።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 21/01/2018፡- የጠቅላይ ሚኒስትር የምስራቅ አፍሪካ አማካሪው አቶ ጌታቸው ረዳ ለሕክምና በዱባይ ሆኖ Global Power Shift ለተሰኘው የዜና ማእከል የሰጡት ቃለ ምልልስ ብዙዎች እያነጋገረ ነው።

አቶ ጌታቸው ካነሱዋቸው ጉዳያች አንዱ የህወሐትና ሻዕቢያ አመራሮች ግንኙነት የተመለከተ ሲሆን “የህወሐት አመራሮች  ከፌደራል መንግስት ይመጣል ብለው ከሚያስቡት እውነተኛ ወይም ምናባዊ ስጋት እራሳቸውን ለማዳን፣ ከኤርትራውያን ጋር ህብረት መፍጠር ይቻል እንደሆነ ማየት ነው” ብሏል።

“ኤርትራውያን በጣም ብልሆች ናቸው። የፌደራል መንግስትን በቀጥታ የመዋጋት የሰው ኃይል ብልጫ እንደሌላቸው ያውቃሉ። ስለዚህ፣ ሀገሪቱን ለማናጋት በድንበራቸው ማዶ ያሉ የፖለቲካ መጠቀሚያዎችን (useful idiots) መጠቀም ይፈልጋሉ” ሲሉም ተደምጧል አቶ ጌታቸው ረዳ።

“የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት በነበርኩበት ወቅት፣ ከኤርትራውያን ጋር ግንኙነት ጀምሬ ነበር ያሉት ሚኒስትሩ ተስፋዬም፣ ሌላ ዙር ጦርነት በትግራይ ላይ እንዳይከሰት መከላከል ነበር፤ ምክንያቱም ለትግራይ ሕዝብ የማይሽር ጠባሳ እንደሚተው ነበር የማየው” ብሏል።

“የህወሓት አመራሮች በትግራይ ህዝብ ዋጋ ሻዕቢያን ለማዳን የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለማቆም መስዋእትነት መክፈል ካለብኝ እከፍላለሁ” ሲሉም ተደምጧል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates