አፍሪካኢትዮጵያፖለቲካ

ከ12 ሺሕ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ::

ኢትዮ ሞኒተር፡ 30/1/2017፡ ሐሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት በሕገ-ወጥ መንገድ ሀገር ውስጥ ገብተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ12 ሺሕ 127 በላይ የውጭ ሀገር  ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል::

ከውጭ ሀገር ዜጎቹ በተጨማሪ፤ ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተገናኘ ዜጎችን ለእንግልት የዳረጉና ብልሹ አሰራር ውስጥ የተገኙ 26 የተቋሙ ሠራተኞች በሕግ ተጠያቂ መደረጋቸው ተነግሯል፡፡

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት 3 ሺሕ 868 ሰዎች የተጭበረበረ ሰነድ በመጠቀም ፓስፖርት ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር በማዋል በሕግ ተጠያቂ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

ባለፉው አንድ ዓመት በቁጥጥር ሥር ከዋሉ ሰዎች መካከል 2 ሺሕ 77 ሃሰተኛ ሰነድ በማቅረብ፣ 275 ኢትዮጵያዊ ሳይሆኑ ፓስፖርት ለማውጣት በመሞከር እንዲሁም የተቀሩት በተለያየ መንገድ ለማጭበርበር ሲሞክሩ የተያዙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates