ኢትዮጵያኢኮኖሚ

ከኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ የሚወጣው ገንዘብ ከጠቅላላ ምርት 2.2 በመቶውን እንደሚያሳጣ የአፍሪካ ልማት ባንክ አስታወቀ ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 30/1/2017፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ በተገባደደው ዓመት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ሁኔታ በሚመለከት ይፋ ባደረገው ሪፖርት፣ ከ55 እስከ 80 በመቶ የሚሆነው ከኢትዮጵያ የሚወጣው ገንዘብ፣ ሕጋዊ ባልሆነ የገቢና የወጪ ንግድ ልውውጥ በኩል ነው።

ይህም ከጠቅላላ የአገሪቱ ምርት (GDP) 2.2 በመቶ ያሳጣታል ብሏል፡፡ እንዲሁም ከስድስት እስከ 23 በመቶ የሚሆነውን አጠቃላይ የኢትዮጵያ ንግድ የሚሸፍን መሆኑን አስታወቀ፡፡

በሕገወጥ መንገድ የሚደረገው የገንዘብ ፍልሰት ከአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት 2.2 በመቶውን እንደሚያሳጣ የሚገልጸው ሪፖርቱ፣ ይህም ከአሥር እስከ 30 በመቶ የመንግሥት ገቢ እንደሆነ ያሳያል፡፡

ለሕገወጥ የገንዘብ ፍልሰቱ ሦስት ምክንያቶች መኖራቸውን የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ የመጀመሪያው ወደ ውጪ የሚላኩ ዕቃዎች ከሚያወጡት ገንዘብ በታች እንደሆነ የሚያስመስል ደረሰኝ ማቅረብ ዋነኛው ነው።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates