አፍሪካ
የሱዳን ኃይሎች ድል አስመዘገብን አሉ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 30/1/2017፡ የሱዳን መንግስት ሃይሎች በሰሜን ኮርዶፋን ሰሜን ኤል-ኦበይድ የምትገኘውን ኡሙ ሳሚማ ከከባድ ውጊያ በኋላ መልሰው መቆጣጠራቸው አስታወቁ።
የተለያዩ ሚድያውች እንደዘገቡት ከሆነ 232 የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ታጣቂዎች መገደላቸው፣ 22 የውጊያ መኪናዎች መማረካቸውና፣ ከ18 በላይ ወድሟል።
በሱዳን ሰራዊትና ፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሓይሉ መካከል እየተካሄደ ያለው ጦርነት በርካታ ሱዳናዊያን ለሞት፣ ረሃብና ስደት እንደዳረገ መረጃዎች ያሳያሉ። ሁለቱም ሐይሎች የየራሳቸው ትዩዩ መንግስት ያቋቋሙ ሲሆን ሱዳን ለሁለት እንዳትከፈል በርካቶች ስጋታቸው እየገለፁ ይገኛሉ።