ኢትዮጵያዲፕሎማሲ

የኢትዮጵያ መንግስት ለአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደብዳቤ መፃፉ ታወቀ።

የደብዳቤው ይዘት ደግሞ ስለኤርትራ ጉዳይ ነው።

ኢትዮሞኒተር፡ 27/10/2017፡ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ ለአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በጻፈው ደብዳቤ የኤርትራ መንግስትን በጦርነት ቀስቃሽነት እና በግዛት ጥሰት ከሰዋል።

በውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ፊርማ የወጣው ደብዳቤው ኤርትራ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት መናድ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ማገድ፣ የመገናኛ መስመሮችን በማስተጓጎል እና የኢትዮጵያን ግዛት እንደያዘች መቀጠሏን ይገልጻል።

የኤርትራ መንግስት በተደጋጋሚ የጦርነት ትንኮሳዎች እያደረገ መሆኑን ደብዳቤው ይከሳል።
የኤርትራ መንግስት በበኩሉ ኤርትራ የጦርነት ፕሮፖጋንዳ ከፍታብኛለች በማለት ይወቅሳል። ስለ ኢትዮጵያ ሉአላዊነት የሚቀርብበት ክስ ሲመልስ በአልጀረስ ስምምነት መሰረት የተሰጠኝ ቦታ ላይ ነኝ በማለት ያስተባብላል። ይልቁኑም ኢትዮጵያ ሉአላዊ ግዛቴን ለ20 ዓመታት ያክል ይዛብኝ ቆይታለች በማለት ተገልብጦ ሲከስ ይሰማል። ይሁን እንጂ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የኤርትራ ሰራዊት ከአልጀርስ ስምምነት ውጪ የትግራይ መሬት ይዞ አሰንደሚገኝ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ትላንት ለፓርላማ በሰጡት ማብራርያ “የኢትዮጵያ መንግስት ወደ ኤርትራ አንድም ጥይት አይተኩስም” ማለታቸው ይታወሳል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates