ፖለቲካ
እስራኤልና ኢራን ተኩስ ያቁሙ – ተመደ

ኢትዮ ሞኒተር፡12/10/2017፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እስራኤል እና ኢራን በ’አፋጣኝ’ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረሱ አሳሰበ።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪክ በሰጡት መግለጫ የኢራን እና የእስራኤል ግጭት እንዳይባባስ አስጠንቅቀዋል። ሁለቱም አገሮች አሁን እያካሄዱት ያሉት ጥቃቶች አቁሞ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ድርድር እንድያደርጉ አሳስቧል። እንዲሁም ማንኛውም አገር ከ’ተጨማሪ ወታደራዊ ጣልቃገብነት’ እንዲቆጠብ አስጠንቅቋል።
እየተባባሰ እየመጣ ያለውን የኢራንና እስራኤል ግጭት ሌሎች አገሮች እነሰዳይገቡበት ተሰግቷል። ሁኔታው ሌሎች አገሮች የሚገቡበት ዕድል ከተፈጠረ ግጭቱ ዓለም አቀፋዊ ይሆናል እየተባለ ነው።