አፍሪካ
ኬንያ የሱዳንን ጦርነትን በማባባስ ረገድ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 11/10/2017፡ ኬንያ በሱዳን እየተካሄደ ያለውን ግጭት በማቀጣጠል ረገድ ሚና እየተጫወተች ነው የሚለውን ክስ ውድቅ አድርጋለች። የኬኒያ መንግስት ቃል አቀባይ ኢሳቅ ሙዋራ የሀገሪቱን ገለልተኛነትና ሰላም ፈላጊነት አቋም አረጋግጠዋል።
የኬንያ ተሳትፎ “ጥብቅ ዲፕሎማሲያዊ ነው” እና ጥረቶቹ “በሱዳን ጦር ኃይሎች እና በፈጣን የድጋፍ ኃይሎች መካከል ሽምግልና እና ሰላም ግንባታ ላይ ያተኮሩ ናቸው” ብለዋል ። “ኬንያ የሱዳን ጦርነት መሐንዲስ አይደለችም፣ በፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በሚመራው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ሂደት ውይይቶችን ለመፍጠር ቁርጠኞች ነን” ብለዋል።
ኬንያ የ2005 አጠቃላይ የሰላም ስምምነትን በመጥቀስ “ከ2019 ጀምሮ ለሱዳን ዲሞክራሲያዊ ሽግግር ድጋፍ የቀጠለችበት የቀጣናውን ሰላም የማመቻቸት ረጅም ታሪክ አላት” ብለዋል። አክለውም ፕሬዝዳንት ሩቶ “በቀጠናዊ ዲፕሎማሲ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል” በማለት ገልጿል።