
ኢትዮ ሞኒተር: 04/10/2017: የባህር በር የሌላት አፍሪካዊ ሀገር ኢ/ያ በሩሲያ እና የተባበሩት ዓረብ ኢሚሬትስ ድጋፍ ዋና የባህር ሃይል አገልግሎት ግንባታ ልታጠናቅቅ ነው ተብሏል።
ኢትዮጵያ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ የሚገኘውን አዲሱን የባህር ሃይል ዋና መሥሪያ ቤት ግንባታን ልታጠናቅቅ መሆኑ ተገልጿል። ይህም ብሄራዊ የባህር ኃይልን መልሶ የማቋቋም ምኞቷን የሚያመላክት መሆኑን ተገልጿል።
ህንፃው በ3 ሄክታር መሬት ያረፈ ሲሆን ባለ አራት ፎቅ ኮምፕሌክስ የአስተዳደር ቢሮዎች፣ የህክምና ክሊኒክ፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና ሌሎች የድጋፍ መሠረተ ልማቶችን ያካተተ ነው ተብሏል።
በመጋቢት 2025 ኢትዮጵያ ከሩሲያ መንግስት ጋር የባህር ኃይል ልማትና ስልጠናን ለመደገፍ የትብብር ስምምነት መፈራርማ ይታወሳል።