
ኢትዮ ሞኒተር፡ 02/10/17፡በአዲስ አበባ ከበርካታ ቀናት የዝግ ስብሰባዎች በኋላ፣ የኤርትራ ህዝቦች ሰማያዊ አብዮታዊ ግንባር (ብርጌድ ንሀመዱ) የተቃውሞ ንቅናቄ ትላንት በይፋ መጀመሩ ተገልጿል።
ግንባሩ በአዲስ አበባ በሰጠው መግለጫ በኤርትራ መንግስት ላይ የተደራጀ ትግል መጀመሩን አስታውቋል።
ይህ የተቃውሞ ግንባር በኢትዮጵያ ምድር በይፋ መጀመሩ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል ባለው የሻከረ ግንኙነት ላይ ሌላ ውጥረት ሊፈጠር እንደሚችል ታዛቢዎች ይጠቅሳሉ።
ብርጌድ ንሃመዱ በአዲስ አበባ ቢሮ መክፈቱንና ስልጠናዎችም መጀመሩ ቀደም ብሎ መረጃዎች ተሰራጭቶ እንደነበሩ ይታወቃል።