ማህበራዊኢትዮጵያ

በኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አዋሳኝ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭቶች ከ11,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለፀ፡፡

የሰብአዊ እርዳታ ኤጀንሲዎች በአከባቢው ውጥረቱ ሊባባስ ይችላል ብለዋል፡፡

 

ኢትዮ ሞኒተር፡ 02/10/17፡- በኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በተፈፀሙ በትጥቅ የተደገፉ ጥቃቶች በሁለት ቀናት ብቻ ከ11,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን የአውሮፓ ኮሚሽን የሲቪል ጥበቃና የሰብአዊ እርዳታ ኦፕሬሽን ኣስታወቀ።

ድርጅቱ ሰሞኑን ባወጣው የሁኔታዎች ሪፖርት፣ መፈናቀሉ የተቀሰቀሰው በትጥቅ ግጭት “በፖለቲካ እና በጎሳ መከፋፈል የተቀሰቀሰ ነው” ሲል በክልሉ ድንበር ላይ ተባብሶ ቀጥሏል ብሏል።

በኦሮሚያ ክልል ሳሲጋ ወረዳ ከምትገኝ ከሀሮዋታ ቀበሌ 5,500 የሚገመቱ ሰዎች ተፈናቅለዋል ሲል ድርጅቱ ኣስታውቀዋል። ኤጀንሲው የተጎዱት ሰላማዊ ሰዎች “አሁን በመንግስት ህንጻዎች ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ” ብሏል።

እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል “ከኦሮሚያ የመጡ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች” በካማሺ ዞን ሁለት ጥቃቶች መፈጸማቸውን የአውሮፓው ሰብአዊ ድርጅት ገልፀዋል። ኤጀንሲው እንዳመለከተው እነዚህ አደጋዎች ወደ 5,900 የሚጠጉ ሰዎችን መፈናቀላቸውን አመልክቷል።

ቢቢሲ ከዚህ ቀደም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን በደረሰ ጥቃት 18 ሰዎች ሲገደሉ አስር ሰዎች መቁሰላቸው ዘግቦ ነበር። አደጋው የተከሰተው እሮብ እ.አ.አ. ግንቦት 21 ቀን 2025 ከቀኑ 5፡00 ሰዓት አካባቢ ነው።

ነዋሪዎች እንደገለፁት ጥቃቱ ከሶጌ ከተማ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኝ አንገር ሜቲ በምትባል ከተማ ላይ ያነጣጠረ ነው። ተጎጂዎቹ “ሰላማዊ ሰዎች ናቸው” ያሉት ነዋሪዎች ጥቃቱን የፈጸሙት “በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ታጣቂዎች ነው” ብሏል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates