ጤና
በኢትዮጵያ በዝንጆሮ ፈንጣጣ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 17 መድረሱ ተገለፀ።

ኢትዮ ሞኒተር
አዲስ አበባ 27/09/2017 :የዝንጀሮ ፈንጣጣ( M pox) በኢትዮጵያ መግባቱ ከተነገረበት ከግንቦት 17 ጀምሮ እስካሁን ለ40 ሰዎች ምርመራ ተደርጎ በ17 ሰዎች ላይ በሽታው መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በበሽታው የአንድ ሰው ህይወት ያለፈ ሲሆን አንድ ሰው ደግሞ ከዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ አገግሟል ተብሏል።
በዝንጀሮ ፈንጣጣ መያዛቸው ከተረጋገጡ ሰዎች መካከል ለ15 ሰዎች በለይቶ ማከሚያ ስፍራ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተገልጿል።
የዝንጆሮ ፈንጣጣ ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች እንደ ሽፍታ፣ ሳል፣ ትኩሳት፣ የራስ ምታት፣ የንፊት ማበጥ፣ የቆዳ ቁስለትና ድካም፣ የጡንቻና የጀርባ ህመም ምልክቶች የሚታይባቸዉ ሲሆን በሽታው በተለይ ታማሚዎች አካል ላይ ቁስል ካለ በቀላሉ የሚተላለፍ ኘው።