አፍሪካኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት አሜሪካ ትደግፋለች – አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ

ኢትዮ ሞኒተር

አዲስ አበባ 27/09/2017 : በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የአሜሪካ መንግስት ይደግፋል አሉ፡፡

ኢትዮጵያ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት እያስመዘገበች መሆኗን ገልጸው÷ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ አሜሪካ ከወሳኝ አጋሯ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንደምትሰራ ተናግረዋል።

አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ኢትዮጵያ ሰፊ የህዝብ ቁጥር ያላት እና ፈጣን ኢኮኖሚ እያስመዘገበች እንደምትገኝ አንስተው÷ ይህ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሚቀጥልም ትንበያ መኖሩን አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በዓለም ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያላትን ህልም ለማሳካት የባህር በር አማራጯን ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው÷ በሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት የአሜሪካ መንግስት የሚደግፈው መሆኑን አረጋግጠዋል።

ኢትዮጵያ ቀጣናው ወደ መረጋጋትና ሰላም እንዲመለስ አስተዋጽኦ እያደረገች መሆኑን አመልክተው÷ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ መስራት አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ያላት ጠንካራ አቋም መሆኑን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በቀጣናው ግዙፍ ብቻ ሳትሆን አቅም እና ተጽዕኖ ያላት ሀገር ነች ያሉት አምባሳደር ማሲንጋ÷ በቀጣናው መረጋጋትና ሰላም ለማስፈን ሀገራቱ በጋራ እንደሚሰሩም መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates