ሱዳን የተባበሩት መንግስታት የፀጥታ ምክር ቤት የፈጣን ድጋፍ ሐይሉ በሽብርተኝነት እንዲፈርጀው ጠየቀች፡፡
የተባበሩት ዓረብ ኢሚሬትስ በሱዳን ህዝብ ላይ ክሕደት እየፈፀመች ነው ስትልም ከሳለች፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 13/06/2018፡- ሱዳን በተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ምክር ቤት፡ ፈጣን የድጋፍ ሚሊሻዎችን እንደ አሸባሪ ድርጅት መመደብ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና በቀጠናው ጦርነት የሚያቀጣጥሉት አካላት ጣልቃ ገብነታቸው እንድያቆሙ ጠየቀች፡፡
በተባበሩት መንግስታት የሱዳን ቋሚ ተወካይ አል-ሃሪዝ ኢድሪስ በተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ምክር ቤት ፊት ባደረጉት ጠንከር ያለ ንግግር፣ የፈጣን ድጋፍ ሐይል ሚሊሻዎችን እንደ አሸባሪ ድርጅት በመመደብ እና ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ከሌሎች የክልል ስፖንሰሮች የሚመጣውን የጦር መሳሪያ እና ወታደራዊ ድጋፍ በማቆም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ወሳኝ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የፖለቲካ ክህደት፣ የሞራል ውድቀት እና ህዝባችን ከህሊናው ሊሰርዘው የማይችል የሀፍረት የለሽ እድፍ ምልክት በመሆና በህዝባችን መታሰቢያ ውስጥ ትቆያለች ብለዋል።
ኢድሪስ ግጭቱን እንደ ውስጣዊ የስልጣን ትግል ሳይሆን ከፈጣን ድጋፍ ሚሊሻ ጋር በተቀናጁ የቀጠናው እና ዓለም አቀፍ ተዋናዮች የሚደገፍት ስልታዊ ጦርነት አድርገው አስቀምጠውታል።
የጦርነቱ ቀጣይነት ከውጪ ወታደራዊ አለመረጋጋት የማይነጣጠል ነው ያሉት ተወካዩ የጦር መሳሪያዎች፣ ድሮኖች፣ የሎጂስቲክስ አውታር መረቦች እና የድንበር ተሻጋሪ ሁኔታ የተመቻቸላቸው ሚሊሻዎች ከበባ እንዲቀጥል፣ ሲቪሎችን ላይ እንዲያነጣጥሩ እና በቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች ትይዩ አስተዳደር እንዲያቋቁሙ አስችሏቸዋል ብለዋል።
የሱዳን ጥያቄ በዘር ማጥፋት፣ ስልታዊ ረሃብ፣ የጎሳ ኢላማ ማድረግ እና በተለይም በኤል ፋሸር እና በዳርፉር በሲቪሎች ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን መሰረት በማድረግ ፈጣን ድጋፍ ሚሊሻው እንደ አሸባሪ ድርጅት መመደብ አለበት የሚል ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
የጸጥታው ምክር ቤቱ በሚሊሻ አመራር ላይ ማዕቀብ እንዲጣል፣ ዓለም አቀፍ የሕግ ተጠያቂነት ዘዴዎችን እንዲያንቀሳቅስ እና በቀጠና የጦር መሳሪያዎችን እና የተራቀቁ ድሮኖችን ስፖንሰርነት እንዲያቆሙ ማዕቀብ እንዲጣልባቸው ጠይቀዋል።



