አፍሪካ

በሱዳን መስጊድ ላይ በደረሰ የድሮን ጥቃት ሕፃናት ተገደሉ

ተፋላሚ ወገኖቹ እርስ በርስ እየተወነጀሉ ነው

ኢትዮ ሞኒተር፡ 05/06/2018፡- በማዕከላዊ ሱዳን በምትገኘው ዋድ ማዳኒ ከተማ በሚገኝ አንድ መስጊድ ላይ ዛሬ ሐሙስ በተፈጸመ የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት ሦስት ሕፃናት መገደላቸውን የሕክምና ባለሙያዎችና የዓይን እማኞች አስታውቀዋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው በሱዳን ጦር እና በከፊል ወታደራዊው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) መካከል ያለው ውጊያ በከረረበት ወቅት ነው።

እንደ የሕክምና ምንጮች ገለጻ ከሆነ ሕፃናቱ ሕይወታቸው ያለፈው መስጊዱ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርት በመከታተል ላይ በነበሩበት ወቅት ነው።

ጥቃቱ የተፈጸመው በገዚራ ግዛት ዋና ከተማ በሆነችው ዋድ ማዳኒ በሚገኝ የመኖሪያ መንደር ውስጥ ሲሆን፤ የአካባቢው ነዋሪዎችና የዋድ ማዳኒ ተቃውሞ ኮሚቴ አባላት እንደሚሉት ከሆነ ከድሮኑ የተለቀቀው መሳሪያ መስጊዱን በቀጥታ መትቶታል።

በዚህም ምክንያት የሦስት ሕፃናት አስከሬን ከፍርስራሹ ውስጥ መገኘቱንና በርካታ ሰዎች ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሕክምና ተቋማት መወሰዳቸውን አረጋግጠዋል።

ድርጊቱ በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት አሁንም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑን የሚያሳይ ነው።

የሱዳን የሕክምና ባለሙያዎች ማኅበር ባወጣው መግለጫ መሠረት ጥቃቱ የተፈጸመው ሰዎች ለጸሎት በሚሰበሰቡበትና ሕፃናት ትምህርት በሚቀስሙበት ስፍራ ላይ መሆኑ ድርጊቱን ይበልጥ አሰቃቂ ያደርገዋል።

ማኅበሩ በጦርነቱ ተሳታፊ የሆኑ ወገኖች የሃይማኖት ተቋማትንና የመኖሪያ መንደሮችን የውጊያ ቀጠና ከማድረግ እንዲቆጠቡ በድጋሚ አሳስቧል።

ይሁን እንጂ ሁለቱም ወገኖች ለዚህ ጥቃት ተጠያቂነትን ከመውሰድ ይልቅ አንዱ ሌላውን የመወንጀል ልምዳቸውን ቀጥለዋል።የፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) “የሱዳን ጦር በንጹሐን ላይ የአየር ጥቃት እየፈጸመ ነው” በማለት ክስ አቅርቧል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates