አፍሪካ

የደቡብ ሱዳን ዜጎች በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ እንደሚገኙ አልጄዚራ አጋለጠ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 04/06/2018፡- የሱዳን ጦር ኃይሎች በታህሳስ መጨረሻ ወር 2025 መጨረሻ ላይ የካዚጊልን የሰሜን ኮርዶፋን ግዛት መልሶ ለማግኘት በተደረገው ውጊያ ከ10 በላይ የደቡብ ሱዳን ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ዘገባው ጠቁመዋል፡፡

የደቡብ ሱዳን ወታደሮች በደቡብ ሱዳን ድንበር ላይ የሚገኘውን የኮርዶፋን ክልል ክፍሎች ከሚገኘው የፈጣን የድጋፍ ኃይሎች (RSF) ጎን ሆነው እየተዋጉ እንደሆኑም ተገልፀዋል።

የደቡብ ሱዳን ተዋጊዎች ከፈጣን ድጋፍ ሐይሉ ጎን ሆኖ በጦርነቱ መሳተፋቸው ተከትሎም የሱዳን መንግስት የደቡብ ሱዳን መንግስት ለማነጋገር እንደተገደደ መረጃው ጠቁመዋል፡፡

የሱዳን ጦር እንደሚለው ከ2024 መጨረሻ ጀምሮ ከደቡብ ሱዳን የመጡ የታጠቁ ቡድኖች ከፈጣን ድጋፍ ሐይሉ ጎን ሆኖ እየተዋጉ ነው።

የደቡብ ሱዳን ዜጎች በጦር ሜዳ ውስጥ መሳተፋቸው በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ውስብስብ ግንኙነት ያሳያል፣ ይህም ምንም እንኳን የራስዋ የእርስ በርስ ጦርነት ሊያጋጥማት እንደሚችል ቢሰጋም ደቡብ ሱዳን ወደ ግጭቱ እየጎተተች እያለች ትመስላለች ይላል ዘገባው፡፡

«በደቡብ ሱዳን ነገሮች ከተበላሹ፣ ይህ በሱዳን የተከሰተውን ጦርነት ከደቡብ ሱዳን ጦርነት ለመለየት በጣም አስቸጋሪ ያደርገዋል» ሲሉ ለዓለም አቀፉ የክራይሲስ ግሩፕ የደቡብ ሱዳን እና የሱዳን ኤክስፐርት የሆኑት አላን ቦስዌል ባለፈው ዓመት ለአልጀዚራ ተናግረዋል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates