ዲፕሎማሲ

የኤርትራ መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት የቀረበለትን ክስ አስተባበለ።

ኢትዮጵያ መንግስት ኤርትራ ወታደሮችዋ ከኢትዮጵያ ግዛት እንድታስወጣ መጠየቁ ይታወሳል፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 02/06/2018፡- የኤርትራ መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት የቀረበለትን ክስ ለድብቅ አጀንዳዎች ያገለግላሉ በማለትም የቀረበለትን ክስ ውድቅ አደረገ።

የኢትዮጵያ መንግስት ኤርትራ ወታደሮችዋ ከኢትዮጵያ ግዛት እንድታስወጣ መጠየቁ ይታወሳል፡፡

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2018 ዓ/ም ባወጣው አጭር መግለጫ “ትላንት በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኤርትራ ላይ ያወጡት ፅሑፍ በግልጽ ሐሰት እና የተፈበረኩ ክሶች ናቸው በማለት በዋናው ተነሳሽነቱ እና በአጠቃላይ ዓላማው አስደናቂ ነው ብሎታል።

 በሚያሳዝን ሁኔታ፣ ከሁለት ዓመታት በላይ በኤርትራ ላይ በተቀሰቀሰ የጠላት ዘመቻ ውስጥ ሌላ አስከፊ ድርጊት በማለት የገለፀው የኤርትራ መግለጫ ቀደም ሲል እንደተገለጸው፣ የኤርትራ መንግስት ነዳጅ ለመጨመር እና ሁኔታውን ለማባባስ ትርጉም በሌለው ውዝግብ ውስጥ ለመሳተፍ ምንም ፍላጎት የለውም በማለት በኢትዮጵያ መንግስት ለወጣው መግለጫ በአጭሩ ግብረ መልስ ሰጥቷል።

 የኢትዮጵያ መንግስት ኤርትራ የኢትዮጵያ የግዛት ወሰንን በመጣስ እና የታጠቁ ቡድኖችን በመደገፍ ረገድ በመክሰስ፤ ወታደሮቿንም እንድታስወጣ ጠይቃለች።

 ኤርትራ ወታደሮቿን ወደ ግዛቷ ዘልቀው እንዲገቡ በማድረግ እና በድንበር አካባቢ ከሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች ጋር በመተባበር ወታደራዊ ትንኮሳ እያባባሰች ነው በማለት ኢትዮጵያ በይፋ የከሰሰች ስትሆን፤ የኤርትራ ኃይሎች በአፋጣኝ እንዲወጡ እና ለታጣቂ ቡድኖች የምታደርገው ማንኛውም ዓይነት ድጋፍ እንድታቆም መጠየቋ ይታወሳል።

የኤርትራ መንግስት በተደጋጋሚ ራሱ ቢከላከልም መሬት ላይ ያለ ሐቅ ግን ሰራዊቱ በኢትዮጵያ ግዛት እንደሚገኝ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ ያረጋገጡት ጉዳይ ነው፡፡

የኤርትራ መንግስት ከፕሪቶሪያው ስምምነት ጀምሮ ይዙዋቸው ከሚገኙ የኢትዮጵያ ግዛቶች በተጨማሪ ሰሙኑን ተጨማሪ አዳዲስ ቦታዎች እንደያዘ መረጃዎች አሳይተዋል፡፡

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates