አፍሪካ

የሱዳን ጦር የደቡብ ኮርዶፋን ዋና ከተማ የሆነችው ካዱግሊ ከፈጣን ድጋፍ ሐይሉ ነፃ ማውጣቱ ገለፀ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 26/05/2018፡- ለሶስት ቀናት ከፈጀ ከባድ ውጊያ በኋላ፣ በተባበሩት አሃዶች የተደገፈው የሱዳን ጦር የደቡብ ኮርዶፋን ዋና ከተማ የሆነችው ከተማ በመቆጣጠር የዳላንግ-ካዱግሊ መንገድን እንደገና ክፍት እንዲሆን ማድረጉን አስታውቋል።

ዛሬ ጠዋት ኃይሎች ወደ ዴይሾል በማቅናት በአል-ኮ አል-ሃሚ እና በአል-ሊሳን ዳቂቅ ላይ ከፍተኛ ውጊያ በማድረግ ወደ ከተማዋ መግባታቸው ታውቋል።

በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሚደገፈው የRSF ሚሊሻ ለመሸሽ ሲሞክር፣ ከአል-ኦቤይድ የተንቀሳቃሽ ኃይል አድፍጦ አብዛኛዎቹን ሰራዊታቸውን አጥፍቶ በርካታ ተዋጊዎችን መያዙ ተዘግቧል።

ይህ ድል የሱዳን ሰራዊት በአሁን ጊዜ በፈጣን ድጋፍ ሐይሉ የበላይነት እየተጎናፀፈ መሆኑን ማሳያ ተደርጎ እየተወሰደ ነው።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates