አውሮፓ

የአውሮፓ ኅብረት የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብን በአሸባሪነት ፈረጀ፡፡

ኢራን ውሳኔውን ታሪካዊ ስህተት በማለት ውድቅ አድርገዋለች፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 22/05/2018፡- ኢራን ባለፉት ሳምንታት ተቃዋሚዎች ላይ የወሰደችውን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን የገደለ እርምጃ ተከትሎ የአውሮፓ ኅብረት የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብን የአሸባሪዎች ዝርዝር ውስጥ አካተተ።

የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ካጃ ካላስ፤ ይህ እርምጃ ኢራን ውስጥ ዋነኛ ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ኃይል የሆነውን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ እንደ አል ቃኢዳ እና ኢስላሚክ ስቴት ያሉ ጂሃዳዊ ቡድኖች ተርታ እንደሚያስቀምጠው ተናግረዋል።

ምክትል ፕሬዝዳንቷ አክለውም፤ “ጭቆና ምላሽ ሳይሰጠው አያልፍም” ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በበኩላቸው የአውሮፓ ኅብረት ውሳኔን “ተውኔታዊ” እና “ጉልህ ስትራቴጂክ ስህተት” ሲሉ ጠርተውታል።

የኅብረቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ባሰፈሩት አጭር መግለጫ፤ “በሺዎች የሚቆጠር የራሱን ሕዝብ የሚገድል የትኛውም አገዛዝ ራሱን ወደ ሞቱ ለመውሰድ እየሠራ ነው” ብለዋል።

ምንም እንኳ አብዮታዊ ዘቡ የአሸባሪዎች ዝርዝር ውስጥ ቢካተትም፤ ምክትል ፕሬዝዳንቷ በኢራን እና በኅብረቱ መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች ክፍት ሆነው ይቆያሉ ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

በአዲሱ ውሳኔ መሠረት የአውሮፓ ኅብረት በስድስት የኢራን ተቋማት እና በአገሪቱ በሚገኙ 15 ሰዎች ላይ ማዕቀብ ተጥሏል።

ማዕቀብ ከተጣለባቸው መካከል የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትሩ እስካንዳር ሞሜኒ፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ሞሐመድ ሞቫሄዲ አዛድ እንዲሁም ዋና ዳኛው ኢማን አፍሻሪ ይገኙበታል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates