አፍሪካ
ኤርትራዊው የሰዎች አዘዋዋሪው የ20 ዓመት እስራት ተፈረደበት።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 20/05/2018፡- የሆላንድ ፍርድ ቤት ኤርትራዊው የሰው አዘዋዋሪው በ20 ዓመት እስራት እንደቀጣ ፈርዶበታል።
ማክሰኞ ዕለት የሆላንድ ፍርድ ቤት ስደተኞች የሚሰቃበት እና ቤተሰቦቻቸው የሚዘረፉበት የሰዎች ዝውውር ቀለበት በመሥራት ተጠርጥሮ ምርመራ ሲደረግበት የቆዮውን አንድ ኤርትራዊ በ20 ዓመት እስራት ፈረደበት።
ፍርድ ቤቱ አማኑኤል ዋሊድ የተባለው ሰው ከኤርትራ ወደ አውሮፓ በሊቢያ በኩል “ያለ ምንም ሰብአዊነት” ስደተኞችን ስያዘዋውር እና ስያሰቃይ እንደነበር ተነግሯል።
“የተሻለ የወደፊት ጊዜ ከሚፈልጉ ሰዎች በተቻለ መጠን ብዙ ገንዘብ ማግኘት ነበር” ሲሉ የፍርድ ቤቱ ዳኛ ሬኔ ሜላርድ ተናግረዋል።
በሰሜናዊው የሆላንድ ከተማ ዝዎሌ የሚገኘው ፍርድ ቤት የወንበዴ አባላት በኔዘርላንድስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በስልክ ሲያወሩ ጥቃትን ለማስቆም ክፍያ ሲጠይቁ ተጎጂዎችን እንዴት እንደሚያሰቃዩ ተሰምቷል ብሏል ፍርድ ቤቱ።
የቤተሰብ አባላት ገንዘብ ካስተላለፉ በኋላ ብቻ ተጎጂዎቹ በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ለነበረው አደገኛ ጉዞ በተንጣለለ ጀልባ ላይ ተጭነዋል፤ ብዙዎቹ በማቋረጥ ላይ ሳሉ ሰጥመዋል ሲል ለፍርዱ ምክንያቶች አስቀምጧል።



