ጤና
ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ በቁጥጥር ስር መዋሉን ይፋ አደረገች።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 18/05/2018፡- አዲስ ኬዝ ሳይታይ ለ42 ቀናት በቁጥጥር ስር መዋሉን አወጀች።
የመጨረሻው ታካሚ ከተገኘ በኋላ ለ42 ተከታታይ ቀናት ምንም አይነት አዲስ ኬዝ ሳይመዘገብ ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ በቁጥጥር ስር መዋሉን በይፋ አስታውቃለች።
የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ዛሬ በተካሄደ መደበኛ ዝግጅት ላይ ባደረጉት ንግግር አዋጁ ብሔራዊ የወረርሽኝ መቆጣጠሪያ መመሪያዎችን እና የዓለም ጤና ድርጅት ደረጃዎችን የሚከተል መሆኑን በመግለጽ በደቡብ ኢትዮጵያ ጂንካ ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው ወረርሽኙ በተሳካ ሁኔታ በቁጥጥር ስር መዋሉን አረጋግጠዋል።
ሚኒስቴሯ እንደገለፁት፣ የመጨረሻው ታካሚ ከተረጋገጠ በኋላ ምንም አይነት አዲስ ኬዝ አልተገኘም፣ ይህም መንግስት ወረርሽኙን በቁጥጥር ስር እንዲውል አስችሎታል ብሏል።



