ፖለቲካ

ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በደቡብ ሱዳን ሰላም እንዲሰፍን አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 08/04/2018፡- የአውሮፓ ኅብረት የልዑካን ቡድን እና የተለያዩ አገራት ዲፕሎማቶች በደቡብ ሱዳን እየታየ ያለው የሰላም እጦት በአስቸኳይ መፍትሔ እንዲያገኝ ሲሉ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።

የልዑካን ቡድኑና የውጭ አገራት መልክተኞቹ በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ በምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ደቡብ ሱዳን ባለው የሰላም ሁኔታ ላይ “ከባድ ሥጋት” እንዳላቸው ገልጸው፤ ችግሩን ለመፍታት ፈጣን እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቅርበዋል።

የልዑካን ቡድኖቹ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር እና ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር በመላ አገሪቱ ሁሉን አቀፍ የሰላም ሂደቶችን እንዲጀምሩ በአጽንኦት አሳስበዋል።

ይህንን የሰላም ጥሪ ያስተላለፉት ከካናዳ፣ ከፈረንሳይ፣ ከጀርመን፣ ከጃፓን፣ ከኖርዌይ፣ ከኔዘርላንድስ፣ ከሱዳን፣ ከኡጋንዳ፣ ከእንግሊዝ እና ከአሜሪካ የተውጣጡ አምባሳደሮችና ተወካዮች ናቸው።

እ.ኤ.አ. በ2011 ከሱዳን ተገንጥላ ነጻነቷን ያወጀችው ደቡብ ሱዳን፣ ገና በለጋነቷ ከ2013 ጀምሮ በማያቋርጥ የእርስ በርስ ግጭት ውስጥ ትገኛለች።

የአናዶሎ ዘገባ እንደሚያመለክተው፣ ይህ የዲፕሎማቶች የጋራ መግለጫ በአገሪቱ እየተባባሰ የመጣውን አለመረጋጋት ለመግታት የታለመ ነው።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates