ዲፕሎማሲ
ኢትዮጵያ እና የተባበሩት ዓረብ ኢሚሬትስ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ለማጎልበት ተስማሙ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 30/04/2018፡- ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከትላንት በስትያ በአዲስ አበባ በከፍተኛ ደረጃ አመራሮች ከተደረጉ ውይይቶች በኋላ አንዳቸው የሌላውን ሰላም፣ ደህንነት፣ የግዛት አንድነት እና የኢኮኖሚ ጥቅም በማስጠበቅ እና በመከላከል ላይ ያተኮሩ “ሁሉን አቀፍ እና ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን” አረጋግጠዋል።
በኢትዮጵያ ባለስልጣናት እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ ሻክቡት ቢን ናህያን አል ናህያን መካከል የተደረገው ውይይት በጋራ መከባበር እና በአስርተ ዓመታት ትብብር ላይ የተመሰረተውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ጥልቀት አጉልቶ አሳይቷል።
በጋራ የሚኒስትሮች መግለጫ ሁለቱም ወገኖች ለቀጠናዊ መረጋጋት ያላቸውን ቁርጠኝነት አጉልተው በመግለጽ በሱዳን በሲቪሎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በማውገዝ፣ ፈጣን የሰብአዊ ተደራሽነት እና ወደ ሲቪል የሚመራ መንግስት ሁሉን አቀፍ ሽግግር እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ የሁለቱም አገሮች ማረጋገጫ የሚመጣው ከጊዜ ወደ ጊዜ ውስብስብ በሆነው የቀጠናው ገጽታ ውስጥ ነው።



