
ኢትዮ ሞኒተር፡ 21/04/2018፡- በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአሜሪካ ምክትል ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ታሚ ብሩስ፣ በሶማሊላንድ ጉዳይ ላይ የአሜሪካ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ለውጥ እንደሌለው ለተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት በይፋ አሳውቁዋል።
አምባሳደሯ በኒውዮርክ በተካሄደው የጸጥታው ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት፣ አሜሪካ ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷን በተመለከተ የምታስታውቀው አዲስ ነገር የለም።
አምባሳደር ታሚ ብሩስ አያይዘውም “በአሜሪካ ፖሊሲ ላይ የተደረገ ምንም ለውጥ የለም” ሲሉ የዋሽንግተንን አቋም ግልጽ አድርገዋል።
አምባሳደሯ የአሜሪካን አቋም ከማስረዳት ባሻገር፣ ስብሰባው መካሄዱን በጠንካራ ቃላት ተቃውመዋል።
የዛሬው ዓይነት ስብሰባዎች በመካከለኛው ምስራቅ እና በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የአለም አቀፍ ሰላም እና ደህንነት ችግር ለመፍታት ከሚደረገው ከባድ ስራ “ትኩረትን የሚሰርቁ” ናቸው ብለዋል።
አምባሳደሯ እስራኤልን በተመለከተ ምክር ቤቱ “ድርብ መስፈርት” ይከተላል ሲሉ ወቅሰዋል።
“እስራኤል ልክ እንደማንኛውም ሉዓላዊ መንግስት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን የማካሄድ እኩል መብት አላት” ያሉት ተወካይዋ፣ ምክር ቤቱ በፍልስጤም ጉዳይ ላይ የነበረውን ዝምታ ከአሁኑ ጋር በማነጻጸር ተችተዋል።
“በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ፣ የዚህ ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ በርካታ ሀገራት፣ የሌለ የፍልስጤም መንግስትን እውቅና ለመስጠት የአንድ ወገን ውሳኔ ሲያሳልፉ፣ ምክር ቤቱ ቁጣውን ለመግለጽ ምንም አይነት አስቸኳይ ስብሰባ አልጠራም” ሲሉ አምባሳደር ብሩስ ተችትዋል።
ምክር ቤቱ በተሳሳተ ጉዳይ ላይ ትኩረት ማድረጉ ተልዕኮውን እያደናቀፈበት ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
በፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ አብዛኞቹ አገሮች የእስራኤል ውሳኔ የምስራቅ አፍሪካና ቀይ ባሕር ቀጠናን ሰላም የሚያደፈርስ ነው በማለት ተቃውሞታል፡፡



