አፍሪካ

ተመድ ቀጣይነት ያለው የጦር መሳሪያዎች ፍሰት የሱዳንን ጦርነት እያቀጣጠለ መሆኑን አስጠነቀቀ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 14/04/2018፡- በሱዳን ውስጥ ገዳይ የሆኑ የጦር መሳሪያዎች አቅርቦት ቀጣይነት ያለው መሆኑ አውዳሚውን ጦርነት እያቀጣጠለው ነው ሲሉ አንድ ከፍተኛ የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣን ገለፁ።

“የጦር መሳሪያዎች አቅርቦት ቀጣይነት ያለው እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተራቀቀ ነው። በዚህም የግጭቱ ዋና አንቀሳቃሽ ሆኖ ቀጥሏል።

ሱዳን በጦር መሳሪያዎች የተሞላች ናት” ሲሉ ረዳት ዋና ፀሐፊ ካሌድ ኪያሪ ለተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ተናግረዋል።

“እነዚህን ፍሰቶች ለማስቆም የሚደረጉ ጥሪዎች ምላሽ አላገኙም፣ እና ምንም አይነት ተጠያቂነት አልታየም።” ሲሉም ወቅሷል።

“ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ወገኖቹ ስምምነት ለማድረግ ወይም ፍጥጫውን ለማላላት ፈቃደኛ አይደሉም። የነዳጅ ገቢን ለመጠበቅ የሚያደርጉትን ትግል ማቆም ቢችሉም፣ እስካሁን ድረስ ህዝባቸውን ለመጠበቅ ተመሳሳይ ነገር ማድረግ አልቻሉም” ሲሉ አክለዋል።

የሽምግልና ጥረቶች በቀጠሉበት ወቅት የፀጥታው ምክር ቤት ጠንካራ እርምጃ እንደሚያስፈልግ አፅንዖት ሰጥተዋል።

“ምክር ቤቱ ግልጽ እና የተባበረ መልእክት እንዲልክ አጥብቀን እንመክራለን፡ ይህንን ጦርነት የሚባብሱ ተጠያቂ ይሁኑ” ሲሉ ኪያሪ ተናግረዋል።

በቅርቡ በኮርዶፋን ክልል የተከሰተውን ጥቃት ለአብነት የጠቀሱት ባለስልጣኑ ይህም በአፀደ ህፃናት እና ሆስፓታል በደረሰው የድሮን ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎችን ተገድሏል፤ ከእነዚህም ውስጥ 63 ሕፃናት ናቸው ብሏል።

ይህ የሲቪሎች ስቃይ “እጅግ በጣም ትልቅ” እና “የማይታሰብ” ሲሉ ጠርተውታል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates