ማህበራዊ

የቻይና አፍሪካ የአቃቤ ህግ የትብብር መድረክ በጓንግዡ መካሄድ ጀመረ።

ኢትዮጵያ በፍትህ ሚኒስትሯ መወከሏ ተሰምቷል።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 19/02/2018፡- የቻይና-አፍሪካ የአቃቤ ህግ የትብብር መድረክ ዛሬ በቻይና ጓንግዡ ግዛት የተጀመረ ሲሆን እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2025 ድረስ ይቀጥላል ሲል የኢትዮጵያ የፍትህ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ኢትዮጵያ በመድረኩ ላይ በፍትህ ሚኒስትር ሃና አራያሴላሴ የሚመራ ልዑክ እንደተወከለችም መረጃው አክሏል።

ልዑኩ በቻይና እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የክስ ትብብርን ለማጠናከር በሚያተኩሩ የተለያዩ ስብሰባዎች ላይ እንደሚሳተፍ ይጠበቃል።
ከመድረኩ በፊት ሚኒስትር ሃና ከቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዪንግ ዮንግ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ማካሄዳቸው ተገልጿል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates