ኢኮኖሚ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት 2 ጊዜ ወደ ሁመራ የበረራ አገልግሎት ሊጀምር እንደሆነ ተገለፀ፡፡

ኢትዮ ሞኒተር፡ 11/02/2018፡- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኅዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዳግም ወደ ሁመራ የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት ሊጀምር መሆኑን መስታወቁን የመንግስት ሚድያዎች ዘግበዋል፡፡

የበረራ አገልግሎቱ በሳምንት 2 ጊዜ እንደሚሆንም አየር መንገዱ አስታውቋል።

የሑመራ አየር መንገድ የሰሜኑ ጦርነት በ2013 ዓ/ም ከተጀመረ ጀምሮ እስካሁን መደበኛ የደንበኞች በረራ አገልግሎት ሰጥቶ አያውቅም፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ውስጥ በ23 ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ከ145 በላይ ወደሆኑ መደረሻዎች የበረራ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates