አፍሪካ

ሶማሌላንድ እና ፑንትላንድ በደህንነት እና የድንበር ተሻጋሪ ንግዶች ለማጠናከር ስምምነት በናይሮቢ መፈራረማቸው ተሰማ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 26/01/2018፡- እ.አ.አ. ከጥቅምት 4 – 5 ከረጅም ዓመታት በኃላ ፊት ለፊት የተገናኙት መሪዎቹ የሶማሊላንድ እና ፑንትላንድ የጋራ የደህንነት እና የትብብር ስምምነት በናይሮቢ ተፈራርመዋል።

በአል-ሸባብ ላይ ለማስተባበር ፣በኤሪጋቮን ለማስታረቅ እና የድንበር ንግድን ለማቃለል ቃል ገብተዋል።

በሁለቱ ቀናት ስብሰባ የሁለቱም ወገኖች ሚኒስትሮችን እና ከፍተኛ የደህንነት ባለስልጣናትን መገኘታቸው ታውቋል።

ይህ “ታሪካዊ” የባለለት ስምምነት “አዲስ የመተማመን መንፈስን ያጎናጽፋል” ተብሏል።

በስምምነቱ መሰረት ሁለቱም ወገኖች ሽብርተኝነትን እና ድንበር ተሻጋሪ ታጣቂዎችን በጋራ ለመዋጋት ቁርጠኛ ሆነዋል።

መሪዎቹ ሰርጎ ገብ ታጣቂ ሐይሎችን ለመከላከል፣ መረጃን ለመለዋወጥ እና ድንበር ጠባቂዎችን ለማስተባበር ቃል ገብተዋል።

እንዲሁም ሁለቱ ወገኖች በባህር ደህንነት፣ የባህር ላይ ወንበዴዎችን እና ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ኢላማ በማድረግ በትብብር እንደሚሰሩ እና በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ንግድን የሚያደፈርሱ የተደራጁ የወንጀል መረቦችን ለመበጣጠስ በጋራ እንደሚታገሉ አስታውቋል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates