አሜሪካአፍሪካ

ፕሬዝዳንት ትራምፕ የሶማሊላንድን የሀገርነት እውቅና ጥያቄ እንደሚያውቁና ውይይት መኖሩንም  ገለጹ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 05/12/2017፡ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአዘርባጃን እና ከአርሜኒያ መሪዎች ጋር በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፣  የሶማሊላንድን ዓለም አቀፍ ዕውቅና የማግኘት የረጅም ጊዜ ጥያቄን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።

ትራምፕ ስለ ሶማሊላንድ ጥያቄ ተጠይቀው ሲመልሱ፣ “ጥሩ ጥያቄ ነው፣ አሁን እየተመለከትነው ነው” ብለዋል፣ ይህም ዩናይትድ ስቴትስ ጉዳዩን በንቃት እያጤነችው መሆኑን ያመለክታል ሲል ሆርን ትሪቢውን ዘግቧል።

ሶማሊላንድ እ.አ.አ ከ1991 ከሶማሊያ ነፃነቷን ካወጀችበት ጊዜ አንስቶ፣ ከሶማሊያ ጋር ሲነፃፀር በተሻለ መረጋጋት እና ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ቢኖራትም፣ ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ መደበኛ ዕውቅና ሳታገኝ ቆይታለች።

የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሐመድ አብዱላሂ እ.አ.አ በ2025 የዓለም መንግስታት ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት፣ እውቅና ማግኘታችን “ቅርብ ነው” ብለው ተስፋቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ለዚህ አሜሪካ ቀዳሚ ልትሆን እንደምትችል ገልጸው ነበር።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates