ኢትዮጵያፖለቲካ

የትግራይ ክልል አመራሮችና ፓለቲከኞች አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት የተጀመረውን ሰላም እንዲያፀኑና ከዳር እንዲያደርሱ ተማፅኖ ቀረበ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 21/11/2017፡ ከኢትዮጵያ 12 ክልሎች እና ሁለት ከተማ መስተዳደሮች የተውጣጡ ከ50 በላይ የሚሆኑ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች እና  ነጋዴዎች ዛሬ ሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ/ም ወደ ትግራይ ተጉዟል።

ከአሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ ጀምሮ በትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር አቀባበል የተደረገላቸው የሰላም ልኡኳኑ “እኛ ስለተቀበላችሁን እናመሰግናለን” ያሉ ሲሆን፣ ጦርነቱን በመፍራት ልዩነቶቻቸውን በውይይት ለመፍታት መምጣታቸውን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ሰላም ትፈልጋለች ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ወደዚህ ከመምጣታችን በፊት ለ15 ቀናት ያህል ተወያይተናል ሲሉም አክለዋል።

” የጀመረው ሰላም እንዲፀና ፤ ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከመስራትና ከመጣር የበለጠ ሃይማኖታዊና አባታዊ ተልእኮ የለንም ለዚህም የሚከፈለውን ሁሉም ዓይነት መስዋእትነት እንከፍላለን ” ብለዋል።

ልዑካኑ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ፣ከህወሓት አመራሮች ፣ተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት ጋር ተገናኝተው ይነጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል። በነገው እለትም በተያዘላቸው መርሃ ግብር ተፈናቃዮቹን በአካል ይጎበኛሉ ተብሏል።
ለተፈናቃዮችም 30 ሚሊዮን ብር ይዞ መጓዛቸው ታውቋል። ከሁለት ሳምንታት በፊት ወደ መቐለ የተጓዙት የአገር ሽማግሌዎች የትግራይ ተፈናቃዮችን ሳይጎቦኙ መመለሳቸው ብዙ ትችት ሲቀርብባቸው እንደነበር ይታወሳል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates