አፍሪካዲፕሎማሲ

ሶማሊያ የግብፅ ጦር በማስፈር በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር ያቀደችውን ዕቅድ በጌዲኦ ውጥረት እንደፈጠረ ተገለፀ።

ኢትዮ ሞኒተር፡ 30/1/2017፡ ቪላ ሶማሊያ የግብፅ ወታደሮችን ለማሰማራት በጌዲኦ ክልል ወታደራዊ ሰፈር ለማቋቋም ቅድሚያ ሰጥታ እየሰራች ነው በማለት በርካታ ሶማሊያዊያን ተቃውማቸው እያሰሙ እንደሚገኙ የባይደዋ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።

ይህ እርምጃ በጎረቤት ኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የታለመ ሲሆን ይህም በአካባቢው መረጋጋት ላይ ስጋት ፈጥሯል ይላል ዘገባው።

የሶማሊያ ፌዴራል መንግስት በጌዲኦ ክልል ነዋሪዎች ላይ አዲስ ወታደራዊ ካምፕ ለመፍጠር እያደረገው ያለው ተገቢ አይደለም ሲሉ ይከሳሉ።  ይህ እርምጃ ለ 2026 ምርጫ የፓርላማ ተወካዮችን ለመምረጥ እና ለግብፅ ወታደራዊ ሰፈር ምቹ የሆኑ ዞኖችን ለማቋቋም ሰፊ ስትራቴጂ አካል እንደሆነም ተገልጿል።

የቀድሞ የጁባላንድ አባላት፣ አዲስ ከተሾሙ የፀጥታ መኮንኖች ጋር ተቀናጅተው፣ የፌደራል መንግስትን አላማዎች መሬት ላይ ለማስፈጸም ከወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ጋር በአየር ይወሰዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም መረጃው አክሏል።

Show More

Related Articles

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  (To Type in English, deselect the checkbox. Read more here)
Back to top button
Lingual Support by India Fascinates