
ኢትዮ ሞኒተር፡ 11/10/2017፡ የኢትዮጵያ መንግስት የትግራይ ግዛት የወረረውን ሃይል በአስቸኳይ እንዲያስወጣም ጠይቋል። ህወሓት ባወጣው ሳምንታዊ መግለጫ ላለፉት አመታት በትዕግስት ሲጠባበቅ የነበረው የትግራይ ህዝብ ወደ ቀያቸው ለመመለስ እየደረሰ ያለው ስቃይ ከሚሸከመው በላይ ነው ብሏል። የኢትዮጵያ መንግስት ወራሪ ሃይሉን ከትግራይ ሉዓላዊ ግዛት በማስወጣት፣ ሰፋሪዎችን ከሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በማውጣት የስነ-ሕዝብ ለውጥ ለማምጣት የሚደረገውን ጥረት በማስቆም የተፈናቀሉ ዜጎችን በሰላም ለመመለስ አፋጣኝ ምላሽ ሊሰጥ ይገባል ብለዋል። ተደራዳሪ አካላት እና የአለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነትን ከመቼውም ጊዜ በላይ ተግባራዊ እንዲያደርግ ጫና እንድያደርጉም ህወሓት ጥሪ አቅርቧል። ህወሓት የአፍሪካ ህብረትን በአስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራና የስምምነቱ አፈጻጸም እንዲገመግም ጠይቋል።